Wednesday, August 27, 2008

ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ ብድር የተገዛ የቧንቧ እቃ በጅቡቲ ወደብ ተወረሰ

Tuesday, 26 August 2008


በተሾመ ንቁ

ለሐረር የመጠጥ ውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ ብድር የተገዛ የቧንቧ ቁሳቁስ በጅቡቲ ወደብ መወረሱ ታወቀ፡፡ ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ አለመጠናቀቁም ታውቋል፡፡

በውሃ ሃብት ሚኒስቴር ተቆጣጣሪነት የተገዛው ለሐረሪ ከተማ የመጠጥ ውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የሚውለው ቧንቧና የቧንቧ መለዋወጫ ቁሳቁስ በጅቡቲ ወደብ መወረሱን የሪፖርተር ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በምንጮቻችን ገለፃ መሰረት ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ የብድር ገንዘብ የተገዛው ቧንቧ በወደቡ ባለቤቶች ተወርሷል፡፡

የቧንቧ ቁሳቁሱን ለመግዛትና ሐረር ከተማ ድረስ ለማቅረብ ጨረታውን ያሸነፈው ዋት ኢንተርናሽናል የተባለ አገር በቀል ድርጅት እቃውን በውሉ መሰረት አላቀረበም፡፡ እንደ ምንጮቻችን ገለፃ ድርጅቱ ጨረታውን በማሸነፉ ከ28 ሚሊዮን ብር በላይ የቅድመ ክፍያ ገንዘብ ወስዷል፡፡ በውሉ መሰረት ድርጅቱ እቃውን በመግዛት በጅቡቲ ወደብ መጋዘን ውስጥ ለረዥም ጊዜ ማስቀመጡና የወደብ ኪራዩ ከእቃው ዋጋ በላይ በመሆኑ መወረሱ ተገልጿል፡፡

የወደቡ አስተዳዳሪ ዱባይ ኢንተርናሽናል እቃው ባለመነሳቱ እቃውን በመውረስ መሸጡ ታውቋል፡፡ የወደቡ አስተዳዳሪ የተወረሰውን ቧንቧ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ነጋዴዎች በጨረታ መሸጡንም በጨረታው ከተካፈሉ ነጋዴዎች ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ለተወረሰው የቧንቧ ዕቃ መግዣ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቀሱት ምንጮቻችን፤ የፌዴራል መስሪያ ቤቱ ፕሮጀክቱን ከመከታተል አኳያ ድክመት እንደታየበት ጠቁመዋል፡፡ ከአፍሪካ ልማት ባንክ የብድር ፈቃድ ለማግኘት ከአንድ ዓመት በላይ እንደሚፈጅ በመጥቀስ ከፍተኛ የጊዜ ክስረት መድረሱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም መሰል ብድር ለማግኘትና የግዢ ጨረታ ለማውጣት በሚደረግ ጥረት ፕሮጀክቱ እንደሚጓተት አስታውቀዋል፡፡

የግዢ ጨረታው አለም አቀፍ ደረጃ በመሆኑ ለጨረታው የወጣው ወጪ መክሰሩን፣ ፕሮጀክቱ ተፈፃሚ ቢሆን ከሐረር ከተማ በተጨማሪ የሀሮማያ፣ የአወዳይ፣ የአዴላና የደንገጎ ከተሞች ተጠቃሚ ይሆኑ እንደነበር ነገር ግን ሳይሳካ መዘግየቱን ጠቁመዋል፡፡

ፕሮጀክቱ ሐምሌ 1997 ሲጀመር በ20 ወራት ጊዜ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደነበረ ያወሱት ምንጮቻችን እስከ አሁን ባለመጠናቀቁ ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የሐረር የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የእቅድና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ቡሽራ መሀመድረሺድ ባለስልጣኑ ጉዳዩን እንደማያውቅ ገልፀዋል፡፡ ባለስልጣኑ የቧንቧ ግዢውም ሆነ የፕሮጀክቱን ሁኔታን እንደማይመለከተው አስታውቀዋል፡፡ አቶ ቡሽራ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚገዛው ቧንቧ በቅርቡ ወደ ሐረር ከተማ ይገባል በሚል እየተጠባበቁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በፌዴራል የውሃ ሀብት ሚኒስቴር የሐረር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ታምራት ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ አለመጠናቀቁን አምነዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ከ71 ኪሎ ሜትር በላይ የሚፈጅ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ የካሳ ክፍያ ሂደት ጊዜ መፍጀቱን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ ቁሳቁስ ግዢ ሂደት ላይ የተፈጠረ መዘግየት፣ በዲዛይን ሥራ ላይ በተከሰተ ችግር፣ በሲሚንቶ እጥረት ምክንያት የኮንስትራክሽን ሥራ መደናቀፉን ጠቅሰዋል፡፡

አቶ ጌታቸው በተጠቀሱት ምክንያቶች ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ አለመጠናቀቁንና በሚቀጥለው መስከረም ወር ውስጥ እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል፡፡ በጅቡቲ ወደብ ስለተወረሰው የፕሮጀክቱ እቃን በተመለከተ የማይመለከታቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

Sunday, August 10, 2008

Hadid's general assembly meeting.

I have some news of hadid. Today they had a meeting of their general assembly. They were around 120 attendants, of whom 80 were the members of the general assembly, 40 of them were representatives of the Ethiopian Electoral Board. On their meeting they democratically elected 15 central committee members. I got their names and you will find it below this letter.



I want also to congratulate all the 15 central committee members. In addition, I hopefully think they will bring change to our society. Further more, these 15 committee members elected 7 executive members among themselves. The meeting and the ceremony was very nice, and the atmosphere of the meeting was excellent. They had all one spirit. That was to bring change to the under served society of Harari people.



Here are the names of the 15 central committee members,

1. President Abdi Sebri
2. Vise President Adil Abdella
3. Secretary Eliyas Taha
4. Hanan Mohammed
5. Abdulwasi Kelifa
6. Fatuma Oumer
7. Salahadin Abdulhafiz
8. Ridwan Bedri
9. Amira Abdosh
10. Adem Abdurehim
11. Abdulfetah Mohammed
12. Abdulwahid Yonis
13. Abdurehman Adem
14. Kelifa Oumer
15. Hashim Salih



From the above committee the seven elected executive members are-

1. President Abdi Sebri

2. Vise President Adil Abdella

3. Secretary Eliyas Taha

4. Hanan Mohammed

5. Ridwan Bedri

6. Salahadin Abdulhafiz

7. Hashim Salih



Finally, I ask Allah to strengthen them to bring change and justice to our society. And for further explanation of about today's event and general information about HADID please be online with paltalk tonight 8:00 pm Ethiopian local time so that you will have more knowledge about this party.


Sami.

Friday, August 08, 2008

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት 183 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በጀትና ዓዋጆችን አጸደቀ

ሐረር, ሐምሌ 30 ቀን 2000 (ሀረር) - የሐረሪ ክልል ምክር ቤት አራተኛ ዓመት አንደኛ መደበኛ ጉባዔ ለ2001 በጀት ዓመት የሚውል 183ነጥብ6 ሚሊዮን ብር በጀት፣ዓዋጆችና ሹመት በማጽደቅ ዛሬ ተጠናቀቀ።

ጉበዔው ለሁለት ቀናት ባካሄደው ጉባዔ በጀቱን ያጸደቀው የክልሉ ምጣኔ ሀብታዊና ማህበራዊ ችግሮች ለማቃለል በዘላቂነት ለማቃለል የሚያስችሉና የኅብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የሚያበቁ ተግባራትን ለማከናወን መሆኑን በጉባዔው ላይ ከቀረበው ማብራሪያ ለመረዳት ተችሏል።

ከበጀቱ 116 ሚሊዮን ብር ለመደበኛ የተመደበ ሲሆን ቀሪው ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ እንደሚውልም ተገልጿል።

ከበጀቱ የክልሉ መንግሥት 42 ሚሊዮን ብር ሲያሰባስብ ጉድለቱ ከፌዴረል መንግሥት ከሚገኝ ድጎማ እንደሚሟላ ተብራርቷል።

እንዲሁም የሐረር ከተማን ዕድገት ለማስጠበቅና የክልሉን የቤተሰብ ሕግ ዓዋጆችና የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሹመት አጽድቋል።

የሐረሪ ክልል ምክር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙራድ አብዱልሐዲ ባደረጉት ንግግር በክልሉ ባለፉት ዓመታት በድህነት ላይ የተመዘገበውን ውጤት በያዝነው የበጀት ዓመትም ለመድገም በጀቱን ወጪ ቆጣቢ በሆነ አሰራርና የኅብረተሰቡን ጉልበት በመጠቀም ለማልማት አስፈጻሚ አካላት መረባረብ እንዳለባቸው አሳስበዋዋል።

ሪፖ 12፡10 ኤዲ ከ12፡10 -12፡30

---END---

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ሶስተኛ ዙር አራተኛ አመት አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ተጀመረ

ሀረር, ሐምሌ 29 ቀን 2000 (ሀረር) - የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ሶስተኛ ዙር አራተኛ አመት አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በሀረር ከተማ የክልሉ ምክር ቤት አዳራሽ ተጀመረ ።

በጉባኤዉ መክፈቻ የክልሉ ዋና ኦዲተርና የአፈ ጉባኤዉ ጽህፈት ቤት ያቀረቧቸዉን የ2000 የስራ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በማዳመጥ በሪፖርቶቹ ላይ ተወያየቷል ።

የክልሉ ዋና ኦዲተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ነስረዲን አሊ ለጉባኤዉ ባቀረቡት ሪፖርት በበጀት አመቱ የታየዉ የስራ አፈጻጸም አበረታች እንደነበረና በገቢና ወጪ ሂሳብ አሰራር ላይ ይህ ነዉ የሚባል የጎላ ጉድለት እንዳልታየ አስታዉቀዋል ።

የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አብዱል መሊክ በከር በበኩላቸዉ ባቀረቡት ሪፖርት በበጀት አመቱ የምክር ቤቱን አሰራር ለማጠናክር በተደረገዉ ጥረት አበረታች ተግባራት መከናወናቸዉን አስረድተዋል ።

ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ በክልሉ በየደረጃዉ የሚገኙ ተቋማትን አቅም ለመገንባት ተደረገዉ ጥረት ፍሬያማ ዉጤት እያሰገኘ መሆኑን አስታዉቀዋል ።

በክልሉ እየተካሄደ ያለዉ አበረታች የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በጋራ መንቀሳቀስ እንደሚገባም አፈ ጉባኤዉ አስገንዝበዋል ።

ጉባኤዉ በተጨማሪ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙረድ አብዱል ሀዲና የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዜዳንት አቶ ኤልያስ ያህያ ባቀረቡት የ2000 የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ በመወያየት ጉባኤዉ ሪፖርቱን በሙሉ ድምጽ ተቀብሎታል ።

ጉባኤዉ በነገዉ ዉሎዉ በክልሉ በመሰረታዊ የስራ ሂደት ለዉጥና የሀረር ከተማን ልማት ለማፋጠን እንዲያስችል በተዘጋጀዉ ረቂቅ አዋጅና በሌሎች ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ለጉባኤዉ የወጣዉ መርሀግብር ያመለክታል ።

ሪፖ10፡25 ኤዲከ11፡00 - 11፡20 ጠሰድ = ጥ/አጥ

---END---